የእግዚአብሔር ሐሳብ

Jan 1, 2023    መጋቢ ዘካርያስ በላይ

መልካምን ነገር በሰው ሕይወት ውስጥ የሚጠብቅ እግዚአብሔር ነው። እኛ ፈጥነን የእግዚአብሔርን ነገር እንረሳለን። የመለኮት ሐሳብ በመንፈሱ በሃይል፣በጽኑ ክንድ ነው የሚጠበቀው። ሃያላን ይነሳሉ ይወድቃሉ። የእግዚአብሔር ሐሳብ ግን ይቀጥላል። ለምን? ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሐሳብ ሁልጊዜ የሚጠበቀው በእግዚአብሔር በራሱ ነው።